በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ውድ ወገኖቼ የዚህ ዩቲዩብ መሰረታዊ ዓላማ የሚከተለው ይሆናል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሃይማኖት እውቀት ማስፋፊያ ጠቅላላ ማኅበር ከሚሰጠው አገልግሎት ውስጥ 1ኛ. በYEMM Media 2ተኛ. በ G Meskel Media በመላው ዓለም በቃለ እግዚአብሔር ለመድረስ እንዲሁም የተቸገሩ ገዳማትን እና አድባራትን ለመደገፍ ፣ ችግረኛ ወገኖችንም ለማጽናናት እንድንችል ይህንን ሁለት ዩቲዩብ ከፍተኛል ሰብስክራይብ በማድረግ እንድታግዙን እየጠየቅን ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው በወንጌል አላፍርም ሮሜ ም.1 ቁ.16 ሕያው ቃል ነው ፡፡ 2. ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳስተማረን ስጡ ይሰጣችሁማል ባለው አምላካዊ ቃል መሰረት በሉቃስ ወ. ም.6 ቁ. 38 ይናገራል ይህም ማለት ካለን ሁሉ አካፍለን እኛን ለሚመስሉ ሰዎች በማካፈል የዘላለም ሕይወትን በዋስትና እንደማቆየት ስለሆነ ችግረኛ ወገኖቻችንን የመርዳት ስራ እለት በእለት የምናከናውንበት የተግባር ስራ ነው ፡፡ 3. ሰውና እግዚአብሔርን የምናስታርቅበት የንስሐ የቄደር ጥምቀት በየእለቱ የሚከናወን ሲሆን የጾም፤ የጸሎት፤ የስግደት፤ የምጽዋት ቅኖናዊ ቤተክርስቲያንን በተግባር የምናይበትና ከአምላካችን ከእግዚአብሔር ጋር የምንገናኝበት መረብ ዘርግተን የምናገለግልበት የብዙኃን መገናኛ አገልግሎት የምስራች ወንጌል ነው ፡፡ በመጨረሻም የሰገነት ኪዳነምሕረት ሚዲያ የገዳማችን መልዕክት የሚተላለፍበት ስለሆነ ሰብስክራይብ አድርጉ የማኅበሩ መስራችና የበላይ ኅላፊ ሊቀ/ትጉ/መ/ር ገ/መስቀል ኅ/መስቀል