መዝሙር 23 1: እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም። 2: በለመለመ መስክ ያሳድረኛል፤ በዕረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል። 3: ነፍሴን መለሳት፥ ስለ ስሙም በጽድቅ መንገድ መራኝ። 4: በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ፡ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጸናኑኛል። 5: በፊቴ ገበታን አዘጋጀህልኝ፡ በጠላቶቼ ፊት ለፊት፡ ራሴን በዘይት ቀባህ፥ ጽዋዬም የተረፈ ነው። 6: ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ።