እኛ አንክሮዎች ነን፥ አገልግሎታችንም ለእናንተ ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬዎችን ባሉበት ማድረስ ነው። ስለኦርቶዶክሳዊ ዝማሬዎች ሁሉን እናደርጋለን ብለን ተነስተናል። በመንፈሳዊ ዝማሬ ሥራዎች ውስጥ መልካም የሚባል አሻራ ለማሳረፍ ርምጃ ጀምረናል። የተመረጡና በያሬዳዊ ዝማሬዎች የተቃኙ የቸብቸቦ፥ የንስኃ ዝማሬዎችን ጆሮ ግቡና ዓይነ ግቡ በሆነ መንገድ በበይነመረብ እንዲደርሶ እናደርጋለን። መዝሙራቸውን ከእኛ ጋር ለመሥራት ለወደዱ ዘማሪያን ስልኮቻችን ክፍት ናቸው። ሐይማኖትን ጠብቀን ዓለምን ስለፈጠረ እግዚአብሔር በአንክሮ እናወድሳለን። ስለብርሃነ ዓለም ክርስቶስ፥ ስለብርሐን እናት ቅድስት ድንግል ማርያምም ያለማቋረጥ እንዘምራለን። የጻድቃን ቅዱሳን ሰማዕታትን ገድልና ክብር በመዝሙሮቻችን እንዘክራለን። በእግዚአብሔር ፊት ዘውትር ስለሚማልዱ ቅዱሳን መልአክትም ገናንነት እንዘምራለን። ስለምንወዳት አንዲት ቤተ ክርስቲያናችንም ዘብ እንቆማለን። ስለመዝሙር ሁሉን እናደርጋለን! አንክሮዎች ነን! ይዩን፥ ያድምጡን፣ አብረውን ይሥሩ!