የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት ዋና ዓላማ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ትምህርተ ሃይማኖት፣ ሥርዓተ አምልኮት (ቀኖናት)፣ ታሪክና ቅርስ፣ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት፣ የበጎ አድራጎትና ልማት፣ ወቅታዊ እንቅስቃሴዎች ማሳወቅ፣ ማስተማርና አወንታዊ ለውጥ ማምጣት ሲሆን ብዙኀን መገናኛን በመጠቀም ቤተ ክርስቲያኒቱ ባሏት ዕሴቶች ለሰው ልጅ ድኅነት፣ ሁለተናዊ ጥቅምና ክብር፣ ለሀገር እድገት፣ ሰላምና በጎ ገጽታ የበኵሏን አስተዋጽኦ እንድታደርግ ማስቻል ይሆናል፡፡