የተደሰቱት ደስታቸውን ይገልጹበት፣ ያዘኑ ይጽናኑበት፣ የደከሙ ይበረቱበት፣ በጥበብም ይመረምሩ ያስታውሉም ዘንድ ለተዋህዶ ልጆች ዘተዋህዶ/The tewahido/ ተመሰረተ። "ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለጨለማው አለም ብርሃን ናት"፤ ስለ ሃይማኖታችን ተነሳን ተዋህዶ እናታችንም ብርሃኗን ለአለም ሁሉ ታበራ ዘንድ እኛ ልጆቿ በጽናት ተነሳን ችቦውንም ለኮስን፡፡ ወ ስብሃት ለእግዚአብሄር ወለ ወላዲቱ ድንግል ወለ መስቀሉ ክብር፡፡