سورة العاديات⤵ وَالْعَادِيَاتِ ضَبْحًا እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡ فَالْمُورِيَاتِ قَدْحًا (በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በኾኑትም፤ فَالْمُغِيرَاتِ صُبْحًا በማለዳ ወራሪዎች በኾኑትም፤ فَأَثَرْنَ بِهِ نَقْعًا በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤ فَوَسَطْنَ بِهِ جَمْعًا በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ፡፡ إِنَّ الْإِنسَانَ لِرَبِّهِ لَكَنُودٌ ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡ وَإِنَّهُ لِحُبِّ الْخَيْرِ لَشَدِيدٌ እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው፡፡ وَإِنَّهُ عَلَىٰ ذَٰلِكَ لَشَهِيدٌ እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው፡፡ ۞ أَفَلَا يَعْلَمُ إِذَا بُعْثِرَ مَا فِي الْقُبُورِ (ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤ وَحُصِّلَ مَا فِي الصُّدُورِ በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚኾን)፡፡ إِنَّ رَبَّهُم بِهِمْ يَوْمَئِذٍ لَّخَبِيرٌ ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡ Share ⤵GOING ⤵ https://t.me/joinchat/AAAAAEVPgqswi5WpcwtkTw