አሁን ብሮድካስቲንግ ካምፓኒ በሀገራችን የሚታየውን የመረጃ ክፍተት ለመሙላት እንዲሁም በማህበራዊ በፖለቲካዊና በኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለሀገርና ለህዝብ የሚጠቅሙ ሀሳቦች በነጻነት ለህዝብ የሚቀርቡበትን መድረክ ለማመቻቸት የተቋቋመ ብሮድካስቲንግ ካምፓኒ ነው። የካምፓኒያችንን ስያሜ ‘’ አሁን ‘’ ብለን ስንነሳ አሁናዊውን የሃገርና የህዝብ መሬት ወረድ እውነታ በመገንዘብና እንደዜጋ በተሰማራንበት የጋዜጠኝነት ሞያ የበኩላችንን ኃላፊነት ለመወጣት በማሰብ ነው። ድርጅታችን አሁን ብሮድካስቲንግ ካምፓኒ ከየትኛውም አይነት ተቋማዊ ፣ቡድናዊም ሆነ ግለሰባዊ ወገንተኝነት የጸዳ በኢትዮጵያዊነት የማይደራደር ከእውነት ጋር ስለእውነት የቆመ ተቋም ነው። በነጻነት ማሰብ ተፈጥሯዊ ፀጋ ነው!! ማንም አይሰጥህም ማንም አይነፍግህም!!