እውቀትን መሻት በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው። ኢማሙ ሙሐመድ አልገዛሊ(ረ.ዐ) እንዳሉት እውቀት የእያንዳንዱ ተግባር ፣ ስራ ወይም የእምነት መሰረት ነው። ካለ እውቀት መልካምነትና ደግነት በዚህም ሆነ በመጭው አለም ሊገኝ አይችልም። ስለዚህ እንደተባለው ከእውቀት በላይ ወደ አሏህ የሚያደርስ (የሚያመራ) መንገድ የለም በእውቀት ቢሆን እንጂ። የሰው ልጅ ጌታውን በብቸኝነት እንዳይገዛ ከሚያደርጉት ነገሮች መካከል አንዱ የሰው ልጅ ልብ በድንቁርና ፅልመት መሸፈኑ ነው።እውቀት የሂወት መሠረት ነው። በእውነቱ እውቀት በራሱ ሂወት ነው። እንዲሁም ድንቁርና የሞት መሠረት ሲሆን ድንቁርና በራሱ ደግሞ ሞት ነው።