አለምን ላበሩት❣❣ ባላወኩኝ ምን ነው በጭራሽ ባልሰማው፣ የነብዬን መናቅ ክብሮን ሲያዋርደው፣ ገና በፅንስ ሳሉ ሰላም ለነበሩት፣ በውልደታቸውም ሁሉን ላስደነቁት፣ ለኔ፡ ለኛ ብለው ሁሉን ላደረጉት፣ ሲናቁ ሰማሁኝ ምንም ባላጠፉት፣ ይህ ነወይ ምላሹ ምድርን ላላቁት፣ ለአለም ብርሀን ሆነው ህይወትን ላስዋቡት፣ ይቅርትን ፣እዝነትን ፣ ሰላምን በማለት፣ ህይወትን ያስዋብት በቁርዐን መሪነት፤ ....... ........ ......... . .......... ........ ......... የኔማ ነብዬ እወዶታለሁኝ፣ የሰው ሁሉ አዉራ መሆኖን አውቃለው፣ እኔ ዝም አልልም የእርሶ ስም ሲንቋሸሽ፣ የምሰማው ሁሉ ሰምቼ የት ልሽሽ፣ የተፈጠርኩበት አላማው ይሄ ነው፣ በእንደዚ አይነቱን ቀን ለስሞ እዋጋለው፣ እርሶ ያላህ ነብይ መሆኖን አውቃለው፣ ከጅህልና ያወጡኝ እርሶኖ መሆኖን እመሰክራለው፣ ❤️❤️❤ ውዱ ነብዬ መሀመድ (ሰ.ዐ.ወ)