ቤተልሔም ማለት የእንጀራ ቤት ማለት ነው። ታሪካዊ ሥፍራ ናት። ዳዊትም ተወልዶ ያደገው፣ ለንጉሥነት የተቀባውና ቤተ መንግሥቱም የነበረው በቤተልሔም ነበር። ስለዚህ በእስራኤላዊያን ታሪክ ውስጥ ቤተልሔም የተወለደ «ቤተልሔማዊ ነኝ» ብሎ ራስን ማስተዋወቅ ክብር ነበረው። (ቤተልሔም እንሂድ ሉቃ ፪፥፲፭) "ክርስቶስ ከዳዊት ዘር ዳዊትም ከነበረባት መንደር ከቤተ ልሔም እንዲመጣ ።" (የዮሐንስ ወንጌል 7: 42) * ቤተልሔም የሚበላውና የሚጠጣውን ክርስቶስን አስገኝታለችና፤ * ከቤተልሔም እረፍት፣ሰላም፣መጽናናት፣ደስታ፣ነጻነት በክርስቶስ ኢየሱስ ተገኝቷል። ቤተልሔምም የእኛ ናት መንፈሳዊ ምግብን እናገኝባታለን ይህን ስያሜዋንም አገኘች