"ከአላህ እዝነት ተስፋ አትቁረጡየሰው ልጅ በባህሪው ተሳሳች ነው:: በላጮቹ ደግሞ ቶሎ ከስህተታቸው የሚመለሱት ናቸው:: በጥፋት ላይ መዘውተር እና ወደ አላህ ለመመለስ አቅም ማጣት የአላህን ሰፊ እዝነት እና መሃሪነት መዘንጋትም ነው ::ሰይጣን በመጪው አለም ተስፋ የለውም ሆኖም በዚህች አለም ግን ተስፋ አይቆርጥም:: አማኞች በመጪው አለም ተስፋ አላቸው ነገር ግን በዚህች አለም በገጠማቸው ፈተና እና በሰሩት ሃጥያት ተስፋን ሲቆርጡ ይታያል:: ምናልባት ከሰው ልጅ ተስፋ ይቆረጥ ይሆናል እንጂ ከአላህ እዝነት ግን ተስፋ ፈፅሞ አይቆረጥም:: አላህ (ሱወ) እንዲህ ይለናል ”በላቸው” «እናንተ በነፍሶቻችሁ ላይ ድንበር ያለፋችሁ *”ባሮቼ ሆይ!”* ከአላህ እዝነት ተስፋ አትቁረጡ፡፡ አላህ ኃጢኣቶችን በመላ ይምራልና፡፡ እነሆ እርሱ መሓሪው አዛኙ ነውና፡፡(39፥53)'